ይህ “ከከፍተኛ የደህንነት ኃላፊዎች አፈትልኮ ወጣ” የተባለው መረጃ ለመጀመሪያ ግዜ የደረሰኝ ባለፈው ሳምንት ሲሆን የስልክ ቃለ ምልልስ ይህን ማያያዣ (Link) በመጫን ማዳመጥ ይቻላል። በተደጋጋሚ እንዲህ ያለ የማስጠንቀቂያና ማስፈራሪያ ስለሚደርሰኝ ብዙም ትኩረት አልሰጠሁትም። ባለፈው ሳምንት መረጃውን ያደረሰኝ ግለሰብ ትላንትም በድጋሜ ከአሜሪካ በቀጥታ የስልክ መስመር ደውሎ ስለሁኔታው በዝርዝር ገለፆልኛል። ከግለሰቡ ጋር ያደረኩትን የስልክ ቃለ ምልልስ ቀድቼዋለሁ። ሁለተኛውን የስልክ ቃለ ምልልስ ይህን ማያያዣ (Link) በመጫን ማዳመጥ ይቻላል፡፡
ከላይ የቀረቡት የስልክ ቃለ ምልልሶች የድምፅ ጥራታቸው ዝቅተኛ በመሆኑ የቃለ ምልልሱን ዋና ሃሳብ እንደሚከተለው በአጭሩ እገልፃለሁ። ከላይ የተጠቀሰው ግለሰብ ከከፍተኛ የደህንነት ኃላፊዎች እና የኢህአዴግ ባለስልጣናት ጋር ቅርበት እንዳለው ይናገራል። ለምሳሌ፣ ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ፣ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ ሬድዋን ሁሴን እና ከከፍተኛ የደህንነት ሃላፊዎች ጋር በአካል ተገናኝቶ እንደሚወያይ ገልጿል፡፡ ይህ ውስጥ አዋቂ እንደሚለው፣ በሀገሪቱ ወቅታዊ ፖለቲካ ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርጉ፣ እኔን ጨምሮ በሦስት ፀሃፊዎች ላይ “መወገድ አለባቸው” የሚል ትዕዛዝ መተላለፉን ገልጿል። ከላይ ከተጠቀሰው ግለሰብ በተጨማሪ፣ ለደህንነት ሰዎች ቅርበት ያላቸው ሌሎች ጓደኞቼ “ስዩም ተሾመ መወገድ አለበት” የሚለው ውሳኔ መተላለፉን እንደሰሙ በመጠቆም ስጋታቸውን ገልፀውልኛል።
ይህን ከመስማቴ በፊት፣ ትላንት ጠዋት ብዙ የፌስቡክ ጏደኞቼ ከአሉላ_ሰለሞን ገፅ ላይ የተወሰደ ምስል ልከውልኝ ነበር። ከታች እንደሚታየው አቶ አሉላ ሰለሞን እኔ እንድታሰር በይፋ ጥሪ አቅርቧል። ውስጥ አዋቂው “ከአሉላ ሰለሞን ጋር እንዴት ስዩም ተሾመ ይወገድ ትላለህ” ብሎ ለረጅም ሰዓት እንደተከራከረው በመግለፅ ከፅሁፉ በስተጀርባ ያለውን እውነታ፣ በተለይ የአቶ አሉላ ሰለሞን የፖለቲካ አቋም በግልፅ ያሳያል፡፡ በዚህ መሠረት፣ አቶ አሉላ ሰለሞን እንደ እኔ የተለየ አቋምና አመለካከት የሚያራምዱ ግለሰቦችን ያለምንም ጥፋትና ማስረጃ እንዲታሰሩ በይፋ ጥሪ ከማቅረብ ጀምሮ ያለፍርድ “መገደል አለባቸው” ብሎ እንደሚከራከር ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህም ህግ በሰፈነበት አሜሪካን ሀገር ተቀምጦ በኢትዮጲያኖች ላይ የሽብር ወንጀል እንዲፈፀም ጥሪና ቅስቀሳ እያደረገ እንደመሆኑ በህግ ሊጠየቅ ይገባል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በወቅታዊ የሀገሪቱ ፖለቲካ ሁኔታ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሚታወቀው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶ/ር ሚልኬሳ_ሚደጋ አዲስ አበባ ቦሌ ማተሚያ ቤት አከባቢ ዛሬ ጠዋት ጥቃት እንደተፈፀመበት ተገልጿል።
በዶ/ር ሚልኬሳ ላይ የተቃጣው ጥቃት ከላይ ከተጠቀሰው መረጃ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት እንዳለው ያስታውቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ ከውስጥ አዋቂው ጋር ያደረኩትን የስልክ ቃለ ምልልስን በYouTube እንደሚከተለው አቀናብሬ አውጥቼዋለሁ።
ወይ ጉድ ምን እሚረብሽ ነገር ነው ።
ምንተሻለን ይሆን ?
በጣም ይዘገንናል ።
LikeLiked by 1 person
ሌባ ድሮም እንደፈራ እና እንደተሸማቀቀ ነው ስዩምም ሆነ መሰሎቹ በብእር ነው ህወሃት ጉጅሌውን ያስቀዘኑት ይሄ ሌባ አይሲስ ወያኔ ሚሰራውን ነው ያጣም ጀግኖች ወገኖቼ ጥንቃቄ አርጉ አይዞዋቹ ካልደፈረሰ አይጠራ
LikeLiked by 1 person
Touch them and expect the worest protest. The USA need to also stop Alula propoganda.
LikeLike
ይገርማል!!
LikeLiked by 1 person
This is a well crafted intimidation by TPLF standard. Don’t give a shit, but take care anyways.
LikeLike
Selam Ato Seyoum. I read what you post on FB and I can understand such information could be very distressing. But, I have two points to raise. One, given your extreme views, no doubt you will be in the radar of law enforcement. I am a lawyer myself, and there are possible speeches of yours that might be considered as illegal. So, no surprise that you are being watched, as you should be in my view. Second, I find it bizarre that you relied on calls from oversees to think you could indeed be prepared for extrajudicial killing. Any member of the diaspora could just do that, as they often do equally horrible things. You are also underestimating the government. I could just get ride of you by sending you to jail. It seems, therefore, that you’re deliberately drawing attention, building a reputation by presenting yourself as an agendum of the State. I admire your determination to voice your criticisms etc but you can still do it in a responsible manner. Don’t take it too extreme. Who is benefiting by your extreme speech? Who is listening? What is changing? So, I encourage you to continue doing your job but consider what your extremism could do in the negative sense.
LikeLike
for how long they continue to kill those who oppose their atrocious deeds? it is easy to put handcuff on hand but it’s hard to put shackles on conscious mind, you have made it clear there is no way they can stop you.
LikeLike
This is intimidation crafted by TPLF agents……no need of fear mongering …….seyoum Teshoma this is fake intimidation.
LikeLike