
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የሚታዩትን ለውጦች እንዲሁ በጅምላ መመልከት ችግሮቹን በግልጽ ለመረዳትና ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት አስቸጋሪ ያደርገዋል። ስለዚህ በሀገራችን የተጀመረውን ለውጥ እና የችግሮችን መንስኤዎች መዋቅራዊ በሆነ መልኩ ማየትና የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያን ፖለቲካ በአምስት ደረጃዎች ከፍሎ ማየት ይቻላል። እነሱም 1ኛ፦ የኦሮማራ ጥምረት፣ 2ኛ፦ የኢትዮጵያ አንድነት፣ 3ኛ፦ አከባቢያዊ ትስስር/ትብብር (Regional Integrity)፣ 4ኛ፦ የፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ፣ 5ኛ፦ ዓለምአቀፋዊ ብዙሃንነት (Multilateralim) ናቸው። በሀገራችን የሚታዩ ለውጦችን ከእነዚህ አምስት ደረጃዎች አንፃር በዝርዝር ማየትና የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ ተገቢ ነው። https://youtu.be/Pc1cvibnmCw